ሚያዝያ 27 እና 28 ቀን 2023 ዓ.ም የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የስራ አፈፃፀሙን፣ የአሰራር ጉድለቶችን እና በቀጣይ በሚከናወኑ ተግባራት ማሻሻያ ግብዓት የሚረዱ ግምገማ ለመሰብሰብ ከአለም አቀፍ ወኪሎቹ ጋር አመታዊ ስብሰባ በማካሄድ ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የመጨረሻው ዓመታዊ ስብሰባ የተካሄደው እ.ኤ.አ. በ 2019 በአዲስ አበባ እንደ ነበርና ከዚያ በኋላ በኮቪድ-19 የጉዞ ገደቦች ምክንያት ይህ ከ 4 ዓመታት በኋላ የመጀመሪያው ስብሰባ መሆኑን በመድረኩ ተገልፇል:: የመርከብ ኢንዱስትሪው አጠቃላይ እይታ፣ ባለፉት 4 ዓመታት ኮንቴይነር የማጓጓዝ አዝማሚያ፣ ዲጂታል ማድረግ እና የማጓጓዣ ቅልጥፍና በተሳታፊዎች ይቀርባል። በዓመታዊ መድረኩ ላይ የተገኙት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ የጋራ ውይይትና ግምገማውን የመሩ ሲሆን የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ከዓለም አቀፍ ወኪሎቹ ጋር እያከናወነ ያለውን የሎጅስቲክ ተግባራትን የሚያሻሽሉ የስራ አቅጣጫዎች ሰጥተዋል።
 
 
On the 5th of May 2023, the Ethiopian Shipping and Logistic Service holds an annual meeting with its worldwide agents to review performance, discuss operational shortcomings and devise ways to improve them in future undertakings. The last Ethiopian Shipping and Logistic Service meeting with its agents was held in Addis Ababa in 2019. After that due to Covid-19 travel restrictions, this would be the first meeting after 4 years. The participants will present an overview of the shipping industry, such as the trend of container shipping in the past 4 years, digitization and efficiency in shipping. On the occasion, H.E Dr. Alemu Sime Minister of Transport and Logistics gives directions that improve the accomplishments of ESL with its worldwide agents.
Twitter
Facebook
Instagram